Telegram Group & Telegram Channel
የእኔ ታሪክ ምዕራፍ -2

ክፍል ዘጠኝ

የሕዝቅኤል ሚስት ኤልሳ ወደ ቤቷ ስትመለስ ብቻዋን አልነበረም ከ አንድ ትልቅ እንግዳ ጋ ነበር ። በተለይ ሕዝቅኤልን በጣም ሊያስደነግጥ ከሚችል እንግዳ ጋ......... ከዛ በፊት ቪቪያን እና ሕዝቅኤል ስለወንድሟ ጉዳይ ተነጋግረው ጨርሰዋል። አብረው ሊሄዱ ወስነው ጉዳዩን ዘግተውታል።



ሕዝቅኤል ወደቤት ሲገባ ኤልሳን መጥታ ስላገኛት የናፍቆቱን ካቀፋት በኋላ ቤት ውስጥ ሌላ እንግዳ እንዳለ ተመለከተ። ፊቷን ሲያየው ድንገት ልቡ ድንግጥ አለ። የሚያውቀው ግን የረሳው ፊት.......የት ነበር ማውቃት ..... ብቻ ግን ፈራት ሴትዮዋ ከተቀመጠችበት እየተነሳች ፈገግ አለች ጭራሽ ስትስቅ ደነገጠ ማን ነች??? አለ ለራሱ የሚያውቃት የልጅነት ጓደኛው ሜሮን ነች። እሷን በመርሳቱ ራሱን ታዘበው ሜሪ አላት በማመን እና ባለማመን ውስጥ ሆኖ ሕዝቄ አለችው ፈገግታዋ ከፊቷ ሳይጠፋ.....ለ ረጅም ደቂቃወች ተቃቀፉ ከብዙ አመታት በኋላ ....... ሕዝቅኤል የልጅነቱን ሕይወት አስታወሰ እንደአዲስ የሆነ መሰለው ። ተቀምጠው ትንሽ ካወሩ በኋላ ኤልሳ እንዴት እንዳገኘቻት ነገረችው። (የሔደችው የእውነትም እናቷን አሟት ሳይሆን ሜሮን እና ጓደኞቿን ፍለጋ ነበር በጅምር የቀረውን የሕዝቅኤልን ታሪክ ለመጨረስ........


ሜሮን ካቆመበት ትቀጥለዋለች። ከዛ በኋላ ግን ምን ተፈጠረ ደህና ሆንሽ? ማቲስ ተገኘ? አብርሽስ ደህና ነው? ልጆችስ ወለድሽ? ሕዝቅኤል የጥያቄ መዓት አወረደባት።


ያኔ ልጄን ካጣሁ በኋላ ለብዙ ሳምንታት መንቃት አልቻልኩም ነበር ። ነገር ግን በህልሜ ይሁን በእውኔ ባላውቅም አንድ ሰው እየመጣ እጄን እየያዘ ያለቅስ ነበር። ይቅርታ አድርጊልኝ ሲል ይሰማኛል። ሜሮን ንቂ እባክሽ ተይ እንደዚህ አታድርጊ ይለኛል። ባለቤቴ እንዳልሆነ ግልፅ ነበር።



አንድ ቀን ግን እንዲህ አለ ሜሪ ዛሬ አይንሽን ገልጠሽ ልነግርሽ ያልቻልኩትን ይዤው የምኖረውን ሕመሜን እነግርሻለሁ። እኔ ቤት ውስጥ ምንም ያልጎደለብኝ ልጅ ነኝ ። ግን ፍቅር ጎድሎብኝ ነበር። በጓደኛቼ ተሰድቤያለሁ፣ ተንቄያለሁ፣ በቤተሰቦቼ ተፈጥሮ ምክኒያት የሰወች ማላገጫ ሆኛለሁ። ልጅነቴን እንደ ልጅ አላደግኩም ሲያሾፉብኝ፣ ከልጆች ጋ በተጣላሁ ቁጥር የእግረ አጭር ልጅ እያሉ ሲያሳምሙኝ፣ አባትህኮ እግሩ አንካሳ ነው ሲሉኝ ህመሜን ዋጥ አድርጌው ኖሬያለሁ። ወንድ ልጅ አያለቅስም ሲሉ ታውቂያለሻ ማንም እንዳያየኝ እየተደበቅኩ ደም እንባ አፍስሻለሁ። ያኔ ግን ማንም ዞር ብሎ አላየኝም ቤተሰቦቼም ቢሆኑ ......ልጅ ነበርኩ ፍቅር ያስፈልገኝ ነበር። ግን አጣሁት በእነሱ አልፈርድም ምክኒያቱም ሳዝን አይተውኝ አያውቁማ.....በቃ ራሴን በሙዚቃ ውስጥ ሸፈንኩት። ማንም እንደማይወደኝ ደመደምኩ እኔም ራሴ ራሴን ጠላሁት ። የነበረኝ አማራጭ ራሴን ከሰወች ማራቅ እና ከፍ ከፍ አድርጎ መታየት ነበር። ግን እውነታው እንደ እኔ ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚያይ አለመኖሩ ነው።



በተቀየርኩ ሰዓት መጣሽ ከራስሽም በላይ ትወጅኝ ነበር ። ምን ነበር ያኔ ልጅነቴ ሳይበረዝ ወደ እኔ ብትመጭ የምወደውን ማንነቴን ሳላጣው ባገኝሽ። ግን እድለ ቢስ ነኝ። እኔ ያላገኘሁትን ፍቅር ለ አንቺ ከየት አምጥቼ ልስጥሽ? የፈለግኩት ከቤተሰቦቼ፣ ከጓደኞቼ ፣ ከማህበረሰቡ ያጣሁትን ፍቅር አንቺ ጋ ማግኘት ነበር። ሁልጊዜ እንድትንከባከቢኝ፣ እስከ ፍፃሜ ድረስ ምንም ባደርግሽ እንዳትተይኝ፣ ከእኔ ውጭ ሌላ ሰው ጋ መኖር እንዳትችይ.......ብቻ በጣም ብዙ ነገር ከአንቺ ፈለግኩኝ በምላሹ ግን እኔ ለአንቺ ምንም መስጠት አልፈልግም።ምክኒያቱም ፍቅር ለ እኔ ሽንፈት ነው። ተሸናፊ መሆን ደግሞ አልፈልግም አንዴ ራሴን ከፍ አድርጌ ሰቅየዋለሁ።ለዛም ነው እንደማፈቅርሽ ለ አንቺ እንደተሸነፍኩ አውጥቼ መናገር የማልችለው እና ፍቅሬን ደብቄ መኖርን የመረጥኩት።




አንቺ ግን ግልፅ ነበርሽ።እብድ ነህ በይኝ አወ እብድ ነኝ ያ ጥሩ የነበረ ነገር ግን ማህበረሰቡ ያሳበደው እብድ......ብቻ ሁሉም አለፈ አንቺም ትተሽኝ ሔድሽ እንደምትመለሽ በሙሉ ልቤ አምኜ እጠብቅሽ ነበር። ግን አግብተሽ ተመለስሽ.....እኔኮ ራስ ወዳድ ነኝ ጭራሽ ከባልሽ ተፋቺ እና እኔ ጋ ሁኚ አልኩሽ። አሁን ሁሉንም ተይው ዛሬ እንደተሸነፍኩ ልመንልሽ በሙሉ ልቤ ከማንም በላይ አፈቅርሻለሁ ሜሪ ይሔው ተነሽ ስሚኝ እኔ ጉረኛው ማቲያስ በጣም አፈቅርሻለሁ!!!!! ማቲ ሲያለቅስ የሲቃ ድምፁን ለመጀመሪያ ጊዜ ሰማሁት ግን አይኖቼ መገለጥ አልቻሉም እንባዬ ብቻ ፈሰሰ ማቲ እንደነቃሁ ገባው መሰለኝ ግንባሬን ስሞኝ ተሰወረ። ወዲያው ዶክተሮቹ ተከታትለው ገቡ።.........


ይቀጥላል...........
@nibab_lehiwot



tg-me.com/nibab_lehiwot/166
Create:
Last Update:

የእኔ ታሪክ ምዕራፍ -2

ክፍል ዘጠኝ

የሕዝቅኤል ሚስት ኤልሳ ወደ ቤቷ ስትመለስ ብቻዋን አልነበረም ከ አንድ ትልቅ እንግዳ ጋ ነበር ። በተለይ ሕዝቅኤልን በጣም ሊያስደነግጥ ከሚችል እንግዳ ጋ......... ከዛ በፊት ቪቪያን እና ሕዝቅኤል ስለወንድሟ ጉዳይ ተነጋግረው ጨርሰዋል። አብረው ሊሄዱ ወስነው ጉዳዩን ዘግተውታል።



ሕዝቅኤል ወደቤት ሲገባ ኤልሳን መጥታ ስላገኛት የናፍቆቱን ካቀፋት በኋላ ቤት ውስጥ ሌላ እንግዳ እንዳለ ተመለከተ። ፊቷን ሲያየው ድንገት ልቡ ድንግጥ አለ። የሚያውቀው ግን የረሳው ፊት.......የት ነበር ማውቃት ..... ብቻ ግን ፈራት ሴትዮዋ ከተቀመጠችበት እየተነሳች ፈገግ አለች ጭራሽ ስትስቅ ደነገጠ ማን ነች??? አለ ለራሱ የሚያውቃት የልጅነት ጓደኛው ሜሮን ነች። እሷን በመርሳቱ ራሱን ታዘበው ሜሪ አላት በማመን እና ባለማመን ውስጥ ሆኖ ሕዝቄ አለችው ፈገግታዋ ከፊቷ ሳይጠፋ.....ለ ረጅም ደቂቃወች ተቃቀፉ ከብዙ አመታት በኋላ ....... ሕዝቅኤል የልጅነቱን ሕይወት አስታወሰ እንደአዲስ የሆነ መሰለው ። ተቀምጠው ትንሽ ካወሩ በኋላ ኤልሳ እንዴት እንዳገኘቻት ነገረችው። (የሔደችው የእውነትም እናቷን አሟት ሳይሆን ሜሮን እና ጓደኞቿን ፍለጋ ነበር በጅምር የቀረውን የሕዝቅኤልን ታሪክ ለመጨረስ........


ሜሮን ካቆመበት ትቀጥለዋለች። ከዛ በኋላ ግን ምን ተፈጠረ ደህና ሆንሽ? ማቲስ ተገኘ? አብርሽስ ደህና ነው? ልጆችስ ወለድሽ? ሕዝቅኤል የጥያቄ መዓት አወረደባት።


ያኔ ልጄን ካጣሁ በኋላ ለብዙ ሳምንታት መንቃት አልቻልኩም ነበር ። ነገር ግን በህልሜ ይሁን በእውኔ ባላውቅም አንድ ሰው እየመጣ እጄን እየያዘ ያለቅስ ነበር። ይቅርታ አድርጊልኝ ሲል ይሰማኛል። ሜሮን ንቂ እባክሽ ተይ እንደዚህ አታድርጊ ይለኛል። ባለቤቴ እንዳልሆነ ግልፅ ነበር።



አንድ ቀን ግን እንዲህ አለ ሜሪ ዛሬ አይንሽን ገልጠሽ ልነግርሽ ያልቻልኩትን ይዤው የምኖረውን ሕመሜን እነግርሻለሁ። እኔ ቤት ውስጥ ምንም ያልጎደለብኝ ልጅ ነኝ ። ግን ፍቅር ጎድሎብኝ ነበር። በጓደኛቼ ተሰድቤያለሁ፣ ተንቄያለሁ፣ በቤተሰቦቼ ተፈጥሮ ምክኒያት የሰወች ማላገጫ ሆኛለሁ። ልጅነቴን እንደ ልጅ አላደግኩም ሲያሾፉብኝ፣ ከልጆች ጋ በተጣላሁ ቁጥር የእግረ አጭር ልጅ እያሉ ሲያሳምሙኝ፣ አባትህኮ እግሩ አንካሳ ነው ሲሉኝ ህመሜን ዋጥ አድርጌው ኖሬያለሁ። ወንድ ልጅ አያለቅስም ሲሉ ታውቂያለሻ ማንም እንዳያየኝ እየተደበቅኩ ደም እንባ አፍስሻለሁ። ያኔ ግን ማንም ዞር ብሎ አላየኝም ቤተሰቦቼም ቢሆኑ ......ልጅ ነበርኩ ፍቅር ያስፈልገኝ ነበር። ግን አጣሁት በእነሱ አልፈርድም ምክኒያቱም ሳዝን አይተውኝ አያውቁማ.....በቃ ራሴን በሙዚቃ ውስጥ ሸፈንኩት። ማንም እንደማይወደኝ ደመደምኩ እኔም ራሴ ራሴን ጠላሁት ። የነበረኝ አማራጭ ራሴን ከሰወች ማራቅ እና ከፍ ከፍ አድርጎ መታየት ነበር። ግን እውነታው እንደ እኔ ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚያይ አለመኖሩ ነው።



በተቀየርኩ ሰዓት መጣሽ ከራስሽም በላይ ትወጅኝ ነበር ። ምን ነበር ያኔ ልጅነቴ ሳይበረዝ ወደ እኔ ብትመጭ የምወደውን ማንነቴን ሳላጣው ባገኝሽ። ግን እድለ ቢስ ነኝ። እኔ ያላገኘሁትን ፍቅር ለ አንቺ ከየት አምጥቼ ልስጥሽ? የፈለግኩት ከቤተሰቦቼ፣ ከጓደኞቼ ፣ ከማህበረሰቡ ያጣሁትን ፍቅር አንቺ ጋ ማግኘት ነበር። ሁልጊዜ እንድትንከባከቢኝ፣ እስከ ፍፃሜ ድረስ ምንም ባደርግሽ እንዳትተይኝ፣ ከእኔ ውጭ ሌላ ሰው ጋ መኖር እንዳትችይ.......ብቻ በጣም ብዙ ነገር ከአንቺ ፈለግኩኝ በምላሹ ግን እኔ ለአንቺ ምንም መስጠት አልፈልግም።ምክኒያቱም ፍቅር ለ እኔ ሽንፈት ነው። ተሸናፊ መሆን ደግሞ አልፈልግም አንዴ ራሴን ከፍ አድርጌ ሰቅየዋለሁ።ለዛም ነው እንደማፈቅርሽ ለ አንቺ እንደተሸነፍኩ አውጥቼ መናገር የማልችለው እና ፍቅሬን ደብቄ መኖርን የመረጥኩት።




አንቺ ግን ግልፅ ነበርሽ።እብድ ነህ በይኝ አወ እብድ ነኝ ያ ጥሩ የነበረ ነገር ግን ማህበረሰቡ ያሳበደው እብድ......ብቻ ሁሉም አለፈ አንቺም ትተሽኝ ሔድሽ እንደምትመለሽ በሙሉ ልቤ አምኜ እጠብቅሽ ነበር። ግን አግብተሽ ተመለስሽ.....እኔኮ ራስ ወዳድ ነኝ ጭራሽ ከባልሽ ተፋቺ እና እኔ ጋ ሁኚ አልኩሽ። አሁን ሁሉንም ተይው ዛሬ እንደተሸነፍኩ ልመንልሽ በሙሉ ልቤ ከማንም በላይ አፈቅርሻለሁ ሜሪ ይሔው ተነሽ ስሚኝ እኔ ጉረኛው ማቲያስ በጣም አፈቅርሻለሁ!!!!! ማቲ ሲያለቅስ የሲቃ ድምፁን ለመጀመሪያ ጊዜ ሰማሁት ግን አይኖቼ መገለጥ አልቻሉም እንባዬ ብቻ ፈሰሰ ማቲ እንደነቃሁ ገባው መሰለኝ ግንባሬን ስሞኝ ተሰወረ። ወዲያው ዶክተሮቹ ተከታትለው ገቡ።.........


ይቀጥላል...........
@nibab_lehiwot

BY ሕይወትን - በገፅ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/166

View MORE
Open in Telegram


ሕይወትን በገፅ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram Be The Next Best SPAC

I have no inside knowledge of a potential stock listing of the popular anti-Whatsapp messaging app, Telegram. But I know this much, judging by most people I talk to, especially crypto investors, if Telegram ever went public, people would gobble it up. I know I would. I’m waiting for it. So is Sergei Sergienko, who claims he owns $800,000 of Telegram’s pre-initial coin offering (ICO) tokens. “If Telegram does a SPAC IPO, there would be demand for this issue. It would probably outstrip the interest we saw during the ICO. Why? Because as of right now Telegram looks like a liberal application that can accept anyone - right after WhatsApp and others have turn on the censorship,” he says.

What Is Bitcoin?

Bitcoin is a decentralized digital currency that you can buy, sell and exchange directly, without an intermediary like a bank. Bitcoin’s creator, Satoshi Nakamoto, originally described the need for “an electronic payment system based on cryptographic proof instead of trust.” Each and every Bitcoin transaction that’s ever been made exists on a public ledger accessible to everyone, making transactions hard to reverse and difficult to fake. That’s by design: Core to their decentralized nature, Bitcoins aren’t backed by the government or any issuing institution, and there’s nothing to guarantee their value besides the proof baked in the heart of the system. “The reason why it’s worth money is simply because we, as people, decided it has value—same as gold,” says Anton Mozgovoy, co-founder & CEO of digital financial service company Holyheld.

ሕይወትን በገፅ from jp


Telegram ሕይወትን - በገፅ
FROM USA